በኢትዮጵያ እና በምስራቅ አፍሪካ የሚገኙ የዩኒቨርስቲ እንዲሁም በቅርብ የተመረቁ ተማሪዎችን ከትምህርት ወደ ስራ በአማካሪነት ፣በክህሎት ግንባታ እና በሙያዊ መድረኮች በጥሩ መልኩ እንዲሸጋገሩ መርዳት
የሙያ እድገት ትራክ የተዘጋጀው በአካዳሚክ ትምህርት እና በሙያዊ ዝግጁነት መካከል ያለውን ክፍተት ለማስተካከል ሲሆን ወጣቶች በዛሬው የሥራ ገበያ ውስጥ ለመግባት እንዲሁም ለማደግ የሚያስፈልጋቸውን መሳሪያዎች፣ በራስ መተማመን እና የተግባቦት ክህሎት ዙሪያ እውቀት ያስገነዝባቸዋል። ይህ ትራክ በሙያ እቅድ፣ በሙያዊ ግንኙነት እና በስራ ቦታ ችሎታዎች ላይ የተዋቀረ መመሪያ ይሰጣል። ተሳታፊዎች ከተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ከተውጣጡ አማካሪዎች ጋር ተቀራርበው ሰለ ስራ ቅጥር፣ስለ ስራ ፈጠራ የሚውያዩበት ክፍል ነው።
እራስን ማወቅ፣ የስራ ግቦችን እና ሙያዊ እሴቶችን እና ጥንካሬዎችን መለየት
የቅጥር ክህሎትን፣ የሲቪ አጻጻፍ፣ የቃለ መጠይቅ ዝግጅት፣ የስራ ቦታ ስነምግባር እና ከሰው ጋር የመባባት ክህሎትን ማዳበር
በስራው ዓለም ያሉ ፕሮጀክቶችን ፣ የስራ ፍለጋ ስልቶችን እና የግል ብራንድ መፍጠር ላይ በመማር ተግባራዊ የሚያደርጉበት ደረጃ ነው።
በተዋቀሩ መንገዶች በኢትዮጵያ እና በምስራቅ አፍሪካ ያሉ ወጣቶች ከዩኒቨርስቲ ወደ ስራ የሚሸጋገሩበትን መንገድ ይከፍታል።
ሲቪ መጻፍ ፣ ቃለ መጠይቅ እና ሙያዊ ሥነ-ምግባርን መገንዘብ
የኢንዱስትሪ ባለሙያዎችን እና ልምድ ያላቸውን አማካሪዎችን በቀጥታ ማግኘት
ኢንተርንሽፕ፣ ፍሪላንሲንግ እና የተለያየ የሥራ ዕድል ከሚሰጡ ድርጅቶች ጋር የመገናኘት እድል
ከ18-30 ለሆኑ ወጣቶች
ለዩኒቨርሲቲ/ኮሌጅ ተማሪዎች፣ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ሰልጣኞች እና በቅርቡ ለተመረቁ ወጣቶች
ለ 24 ሳምንታት በሳምንት ከ5-8 ሰአታት መስጠት የሚችሉ
ለሙያዊ እድገት እና አመራር ተነሳሽነት ያላቸው
በክፍት ጊዜ ውስጥ ኦላይን የማመልከቻ ቅጹን ይሙሉ
ቡድናችን ብቁ እና ከፕሮግራሙ ግቦች ጋር መጣጣምን ለማረጋገጥ አመልካቾችን ይገመግማል
እስከ ሃምሌ 15 ድረስ የእርስዎን ተቀባይነት ያገኛሉ