በመላው ኢትዮጵያ እና በምስራቅ አፍሪካ ያሉ ወጣቶችን በተቀናጀ መልኩ የማማከር፣ ሙያዊ ድጋፍ እና የክህሎት ግንባታ እድሎች እምቅ አቅማቸውን እንዲጠቀሙ መደገፍ። የሙያ ወግ የማማከር ፕሮግራሞች ተማሪዎችን፣ ተመራቂዎችን እና ወጣት ስራ ፈጣሪዎችን ያካተተ፣ እንዲሁም ከስራ፣ ፈጠራ እና አመራር ከሚያማክሩና ከሚያንጹ ባለሙያዎች ጋር ያገናኛል።
ከእርስዎ ፍላጎት እና የስራ ጉዞ ጋር የሚስማማውን ዘርፍ ይፈልጉ
ለከፍተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች
ለሁለተኛና ከፍተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች፣ የEUEE ውጤትን በመጠባበቅ ላይ ያሉ በዚህ ዘርፍ ቀዳሚ የሙያ ግንዛቤዎችን፣ የትምህርት ምርጫዎችን እና ለወደፊት ስኬት መሰረታዊ የክህሎት እድገትን ይሰጣል።
ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስና እና ሂሳብ
ስለ ፈጠራ እና STEM መስኮች ጥልቅ ፍላጎት ላላቸው ወጣቶች የተዘጋጀ ሲሆን ይህ ዘርፍ ቴክኖሎጂን እና የምህንድስና ስራዎችን በማማከር፣ በተግባር የተደገፉ ትምህርት እና በፕሮጀክት ላይ የተመሰረተ ልምድን ያገኙበታል።
ወጣት ሴቶችን ማብቃት
በእቴጌ ጣይቱ ተነሳሽነት የተሰየመ ሲሆን ይህ ዘርፍ ወጣት ሴቶችን እራስን በማግኘት እና በሙያዊ እድገት ዙሪያ በማማከር የአመራር እና በራስ መተማመንን ብቃትን ይገነባል። ተሳታፊዎች በማህበረሰባቸው ውስጥ ለመምራት፣ ተጽዕኖ ለመፍጠር እና ለውጥ ለማምጣት የሚያስችላቸውን ምክረ-ሃሳቦችንና እድሎችን ያገኛሉ።
አነስተኛ ንግድ ማበልጸግ
በአነስተኛ ምርትና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ለተሰማሩ ወጣቶች የተዘጋጀ ሲሆን በቢዝነስ መሰረታዊ ቀመሮች፣ ቢዝነስን በማስፋፋት እና ማህበረሰባው ዘላቂነትን ማሳደግ ላይ ያተኩራል።
University Students & Recent Graduates
Supporting university students and recent graduates across Ethiopia and East Africa in transitioning from education to meaningful, dignified careers through mentorship, skill-building, and professional exposure.